አዲስ አበባ የተበላች ዕቁብ!!
(ኤልያስ በቀለ)

አማራ ተስፋው መደራጀት ብቻ ነው ! አንድ መሆን ብቻ ነው! ማንም በሚቀርጽለት ፕሮግራም ሳይሆን የራሱ የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካ፣ ማህበራዊና የሴኪውሪቲ ፐሮግራም ቀርጾ መንገዱን አንድ ብሎ መጀመር አለበት ! ዛሬ እየተንጋጋ የገባው የኦነግ ሰራዊት አገር ብቻ ነው የቀየረው አስተሳሰቡ ያው የትላንቱ ነው!አማራ ጠል!! ዘረኛ ! ኢትዮጲያ የሚል ስም የሚያቃዥው !! በኦነግና በቄሮ መካከል ያለው ልዩነት ምን ይመስልሃል? ምንም! ቄሮ መሳሪያ ያልታጠቀ ኦነግ ነው! ዛሬ በዱላ የዛተባትን አዲስ አበባ ነገ ነፍጥ ተሸክሞ ይመለስባታል!ዛሬ ማፍረስ ነበር ብሎ የተመለሰውን የሚኒሊክ ሃውልት ብቻ ሳይሆን እየተግተለተለ አንኮበር ልዝመት ይላል!! ያኔ በዳቦና በውሃ የምትመልሰው ከመሰልህ ጅል ነህ! አዲስ አበባ የተበላች ቁብ ናት!!ዛሬ አንድም የአዲስ አበባ ነዋሪ ቀና በሎ ህገ መንግስቱ በፈቀደለት መሰረት በድፍረት አዲስ አበባ የራሳችን ናት ማለት አይችልም! መንግስትን ጨመሮ!!

ሁሉም ይሉኝታ ይዞት ሰላም ይሻላል ብሎ አገርና አንድነት የበጃል ብሎ መታገሱ አዲስ አበባን አስበልቶታል! ባሻው ጊዜ ብቅ እያለ የሚያስፈራራው ሃይል ተዘጋጅቶለታል! አሁን ህግ አስፈጻሚ ማለት ባኮረፈ ቁጥር ዱላ ይዞ መንገድ የሚዘጋው ቄሮ ነው! አሁን ፓርላማ ማለት ዝጉ ክፈቱ ግቡ ውጡ እያለ የሚያዘው ጃዋር ነው! ይሄን ሁላችንም እናውቃለን!! ችግሩ ይሄ ብቻ አይደለም የትግራይ አክቲቪስቶች የአዲስ አበባን ህዝብ ዶሮ ሳይጮህ ሶስት ጊዜ ክደውታል! ሴቶች ህጻናት ሚሊየኖች የሚኖርባት አዲስ አበባን ቄሮ በተባለ ቡድን እሳት እንዲለቀቅባት ከበው ድጋፍ ሲሰጡና ሲያጨበጭቡ፣ የሚኒሊክ ሃውልት እንዲፈርስ በዘወርዋራው ሲገፋፉ ደም እንዲፈስ ሲያጃግኑ እዚሁ ፌስቡክ ላይ አይተናል ! ይህ አዲስ አበባ ላይ የሞከሩት እልቂትና የደገሱት እልቂት ትላንት ደርግ ሃውዜን ላይ ፈጸመብን ካሉት ጭፍጨፋ አስር እጥፍ የሚበልጥ ነው!! አሁንም በአዲስ አበባ ዙሪያ ለሚደርሰው ግድያም ሆነ ዘረፋ እነዚህ አክቲቪስቶች ከቄሮ እኩል ተጠያቂ ናቸው !! የሆነ ሁኖ የዚህ ሁሉ ስንክሳር የመጀመሪያ ኢላማ የሆነው አማራ ከመደራጀት ውጭ ሌላ አማራጭ የለውም!

Leave a comment